Latest Articles

  • " ዲሽታግና ".....አዳም ወንድሜ ...!!

    በአንድ ወር ውስጥ የ8.4 ሚሊዮን የተመልካች ቱጃር ሆነ ::

     

      ከአለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ለንደን)                       

     

    የሙዚቃው ኢንዱስትሪ እጅግ በጣም ፈጣን እድገት የሚታይበት፣ ተለዋዋጭና ከፍተኛ ፉክክር ያለበት በመሆኑ ብዙ ድምፃውያን የሙዚቃ ምርጫቻው እንደአሳታሚው ፍላጎት የሚለወጥበትም ጊዜ ያጋጥማቸዋል ::  በዚህ ምክኒያት ዛሬ ተወዳጅ የሆነ ሙዚቃ ቶሎ ይሰለችና፤ አሮጌ ሆኖ ሸልፍ ላይ ይቀመጣል ::  

    አንድ ሙዚቃ ተወዳጅ መሆኑንና አለመሆኑን የሚወስነው  በሙዚቃው አድማጭ በመሆኑ  ሙዚቃውን  የምንመርጥበት መስፈርት ደግሞ ብዙ ነው ::  አንዳንዶቻችን የሙዚቃው ቅንብርና የድምፃዊያኑን ቅላፄ ስናደንቅ ሌሎቻችን  ደግሞ ምቱ ደስ ስላለንና  ግጥሞቹ  ወይንም የሥነ ምግባር እሴቶቻችንም  ግምት ውስጥ  አስገብተን ስለተመቸን  ከሙዚቃው  ቃና ከፍተኛ ኃይል ይልቅ  በስሜታችን ላይ ጥልቅ የሆነ ተጽዕኖ የሚያሳድረው   ጠብቅ፤ የሕይወት ግንኙነት የሚኖረው ግጥሙ ሆኖ እናገኜዋለን  :: 

    ሙዚቃ በሰዎች ጤና እና ባህሪ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ሊኖረው ይችላል የሚለው የባለሞያዎች ምክር እንደተጠበቀ ሆኖ በአለም አቀፍ 

     ተወዳጅ እንዲሆንና በብዛት  እንዲደመጥ እንዲሸጥ ምክኒያት የሚሆነው ግን የወጣቱ  ተሳትፎ ነው ::  በተለይ የግጥምና የዜማ ደራሲዎችም ቢሆኑ በበኩላችው  የሰዎችን ስሜት የሚኮረኩሩ ማለትም በተስፋቸው፣ በሚያልሙት ነገርና በውስጣዊ ስሜታቸው ዙሪያ የሚያጠነጥኑ ስንኞችን ለማዘጋጀት ስለሚጥሩ ወጣቱ ለሙዚቃው ኢንዱስትሪ ማደግ ትልቅ አስተዎፅዎ አድርጏል ::

    ሆኖም ግን በብዙዎች ዘንድ ተቀባይነት ማግኘት የሚችሉና  እድሜ ጠገብ ሆነው የሚዘልቁ በጣም ጥቂት ድምፃዊያን ካልሆኑ በቀር አብዛኛዎቹ ሞያቸውን እርግፍ አርገው  በመተው መድረኩን ጥለው በመውጣት በተለያየ ሞያ ተሰማርተው ይገኛሉ :: ::

     እንደምን አላችሁልኝ ውድ የፌስ ቡክ ወዳጆቼ 

    ለዛሬው ይዤላችሁ የምቀርበው በዩቲዩብ ተለቆ በአንድ ወር እድሜ ውስጥ የ8.4 ተመልካች ቱጃር ስለሆነው  የድምፃዊ ታሪኩ ዲሽታግና

    የኦሪስ ብሔረሰብ ዘፈን ነው ::

    በቅድሚያ የሙዚቃ ግጥሞቹ ሲዘጋጁ የሰውን ልጅ ስሜትና የልብ ትርታ ለመግዛት በፍጥነትና  በዝግመት እየጠበቁ በምርጥ የሙዚቃ ቃናን ተከሽነው አዕምሮአችንን ጠልቀው ለመንካት ለማዝናናት ኃይል እንዲኖራቸው ተደርገው ስለተዘጋጁ አይረሴነት ይዘት አላቸው ::

    በግጥሙ ስንኝና በሙዚቃው ቅንብር ውስጥ የተውኔት ጥበብ፣ይታይበታል ::  

     

    ዲሽታግና የአሪ ብሔረሰብ አዲስ ዓመት ወይም ዘመን መለወጫ ነው። ዲሽታግና አብረን እንብላ፣ አብረን እንጠጣ፣ የተጣሉትን እናስታርቅ ፣ ለሌላቸው እንስጥ፣ እንደጋገፍ ማለት ነው።

      ዲሽታግና  አድማጩን በመወክልና የስንኙ ተዋናይ እንድንሆን የሚደርግ  ሲሆን በሙዚቃው ምት እንቅስቃሴ መላውን የሰውነት አካል እያፍታታ ሲደመጥ ደስ በተሰኙና ቀለል ባሉ ግጥሞቹ እኛንም ሌሎቻችንንም እርስ በእርስ እንድንተያይ  የታሪኩ ባለቤቶች ሁላችንም በማድረግ የተሸሸጉ በርከታ ማንነትን ወደ አንድነት በማምጣት ዘፈኑን አጏጊ አድርጎ እንድንቀላቀልና እራሳችንን እንድንጠይቅ ልብ እንድንገዛ ጭምር በማድረግ ያሳትፋል :': 

    በሌላ አኳያ ዘፈኑ ከሙዚቃው ጋር ተስማምቶ ድምፃዊ ታሪኩ ጋንኪሲ ሊገልፀው  የፈለገውን ፍሬ ነገር   በሚገርም ጥበብ  ለሁሉም የሰው ዘር  እንደሚጥቅም አድርጎ በመልዕክትነቱ  ለማስተላለፍ ችሏል :: 

     በነገራችን ላይ ሙዚቃ በቴክኒክ ቅንብር የዳበረ መሆን ስለሚገባው ድምፃዊው የሚጠበቅበትን ድርሻ በፈጣራው ውስጥ እነዚህን ቴክኒኮች ተጠቅሞ መልዕክቱን አግዝፎና አጉልቶ ሊያስደምጠን ሲችል ብቻ ነውየተዋጣለት ነው የምንለው ::

     

    ዲሽታግና  ስንኙቹ ባይታወር የሚያደርጉ ሳይሆን በምሳሌነት የተጠቀሰው አዳም ወንድሜ ሕይዋን እህቴ  የሰውን ልጅ አፈጣጠር    ተመርኮዞው በሀይማኖትና በዘር ለሚናከስ ማሕበረሰብ በጥልቀት እራሱን እንዲፈትሽ አግዝፈው የሚያስገነዝቡ የፈጠራ ተልእኳቸውን  የሚያሳዩ ናቸው    :: 

    ዲሽታግና  ከዚህም በላቀ ደረጃ አንድን የ10 አመት የጎዳና ታዳጊ ወጣት አቡሽን  ከአደንዛዥ ሱስ ያላቀቀ  ከእውነተኛ የሰው ልጅ ውስጣዊ ስሜት ጋር የጠበቀ ዝምድና ያስገነዘበና የተፈጥሮን ዳኝነት የእውኑን አለም እውነታ በገሀድ ያሳየ በመሆኑ የሕይወት  ሚስጥራዊ ተልዕኮ አለው ማለት ይቻላል :: 

    ዲሽታግና በችግርና በሀዘን የተቆራመደን ታዳጊ ከትካዜና ከቀዘቀዘ ሕይወት በጥልቀት ገብቶ  የብቸኝነት ጥላውን ገፎ ዝምታን አሰብሮ

    በሞቀ ፈገግታ ሽመሉን አስጨብጦ ዳንኬራ ማስመታት ብቻ ሳይሆን ከጎዳና አንስቶ ሕይወቱን ቀይሮታል :: 

    ዲሽታግና በዚህና በብዙ.ምክኒያት ድምጻዊው ታሪኩ ጋንኪሲ

    ማንነትን ያሳየንና የእሱነቱ መገለጫ  ውስጣዊ የፈጠራ ባሕሪውን ጭምር  ሁለተናዊ አስተዋይነቱን አጉልቶ ሊያስነብበን ችሏል  ::

    በበኩሌ የትያትር ጥበብንና የፊልምን ቴክኒዎለጂ አድናቂ እንጅ  ገፋ በሙዚቃ ስራዎችን ላይ ስለማልሳተፍ በግርድፉ ካልሆነ በቀር ብዙም የጠለቀ እውቀት የለኝም ::

    ቢሆንም  በአንድ ወር ውስጥ ከ8..4  ሚሊየን በላይ ተመልካቾችን ያገኘውን ዲሽታግና አለማድነቅ አይቻልም ::

    ቀደም ብየ ከመግቢያዬ ላይ እንደገለፅኩላችሁ ድምፃዊው ታሪኩ ጋንኪሲ በቀላል ስነግጥም በውስጡ የፀነሰውን ሐሳብ ይዞ ለቃላቱ ሳይጨነቅ በዜይባዊ አነጋገሮች አዚሞ ሕብረ ብሔራዊ ቀለም ሰቶታል :: የመጨረሻውን እፁብ፣ድንቅ ከሚሰኙ የይዘትና ቅርፅ ደረጃ ላይ ለመድረስ ማቋረጥ ያለበትን ውስብስብ ሒደት አልፎ ድምፃዊ ታሪኩ በአንድ ነጠላ ዘፈን አንድ የሙዚቃ ሐውልት ቀርፆ አቁሞ አሳይቶናል  ::

    ለዛሬው የጎዳናውን አቡሽና  ድምጻዊው ታሪኩ ጋንኪሲ መልካም እድል የተመኜሁ ዝግጅቴን በዚሁ አበቃሁ :: የተረፈውን እናንተ ጨምሩበት 

     በሌላ ዝግጅት እስክንገኝ ፣ እድሜ ይስጠን ጤና ይስጠን  እሩቅ ካሉት ቅርብም ካሉት ቸር ያሰማን  ደቡብ ፣ ሰሜን ፣ ምዕራብ ፣ ምስራቅ ፣ በቸር አድሮ በቸር ይንጋ

     

    አለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ለንደን)

    Read more
  • የመጨረሻዋ ስዓት !!

    " የመጨረሻዋ ስዓት !! "
    " ከእያንዳንዱ ብርሀን ጀርባ ጨለማ እንዳለ አስተውል፡፡ ያለህበት ብርሀን ዘላቂ ይሆንልህ ዘንድ መልካም ነገሮችን ብቻ አድርግ፡፡
    ክፋት ካከልክበት ከጨለማው ስር ትወድቅና ታሪክ በበጎ አያነሳህም
    ከአለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ለንደ)
    የሰማንያ ዓመት ዕውቀትን ለመገብየት ግድ ሰማንያ ዓመት መኖር የለብንም ። ሰማንያ ዓመት ከኖሩት በትሕትና መጠየቅ ወይንም የታሪክ ድርሳናትን መፈተሽ ይገባናል ።
    የአለማችን ታላላቅ ሰዎች ፀሀይ ስታዘቀዝቅባቸው፣ ጀንበር ሳትጠልቅባቸው በፊት የዚችን ከንቱ ዓለም የመጨረሻዋ ስአት ላይ የሚገርም ስንብት ያደርጋሉ :: ይህ ታሪክ ሲፈፀም ላላዩት ላልሰሙት ታሪክ ምስክርነቱን ሊሰጥ ዛሬ በፊታችሁ ቆሟል ::
    ካነበብኩት አንድ ለመንገድ ልበላችሁ
    ታላቁ አሌክሳንደር በህይወት ዘመኑ ብዙ መንግስታትንና ሀገሮችን በቁጥጥሩ ስር ያደረገ ጀግና ንጉስ ነበር፡፡ አንድ ጊዜ ብዙ ሀገራትን ድል አድርጎ ወደሃገሩ እየተመለሰ ሳለ በጣም አመመዉ፡፡
    የኔ የሚላቸዉ ጀኔራሎቹንና ቁልፍ ሰዎችም እንዲያርፍና ህክምና እንዲከታተል ማድረግ ጀመሩ፡፡ ነገር ግን የሱ ህመም ከቀን ወደቀን እየባሰና ወደሞት አፋፍ እየቀረበ መጣ፡፡
    አንድ ቀን ግን ህመሙ እጅግ ከብዶ በመምጣቱ አሌክሳንደር እንደማይድን አዉቆታል፡፡ ጄነራሎቹን ሁሉ አስጠርቶ ኑዛዜ መናዘዝ ጀመረ... “ስሙኝ...ከደቂቃ በኋላ ወደማልመለስበት እሄዳለሁ ነገር ግን ስሞት ሶስት ነገሮች እንድታደርጉልኝ እፈልጋለሁ አላቸዉ፡፡
    • የመጀመሪያዉ የመቃብር ሳጥኔ እኔን ሲያክሙኝ የነበሩ ዶክተሮች ብቻ ተሸክመዉ ወስደዉ እንዲቀብሩኝ
    • ሁለተኛዉ ወደ መቀበሪያዬ ቦታ የሚወስደዉ መንገድ በወርቅና በከበረ ድንጋይ እንዲሰራ
    • ሶስተኛዉ ደግሞ ሁለቱም እጆቼ ከመቃብር ሳጥኑ ዉጪ እንዲታዩ አዝዣለሁ ብሎ የመጨረሻዎቹን ትንፋሾች መሳብ ጀመረ፡፡
    የንግግሩን ግራ አጋቢነት የከበቡት ዶክተሮችና አገልጋዬች ባይረዱትም ንጉስ ነዉና ሁሉም ዝም ብለዉ እሺታቸዉን ገለፁ፡፡ ነገር ግን በዚህ ግራ የገባዉ የቅርቡ ጀነራል ንጉሱን እንደምንም ብሎ ጠየቀው
    “ንጉስ ሆይ ሶስቱ ኑዛዜህ አልገባኝምና እባክህ ቢቻልህ ምን ማለት እንደሆነ ብትነግረኝ?” ንጉሱም እንዲህ አለዉ
    “ሁሉም ሰዉ እንዲያዉቅልኝ የምፈልገዉ ሶስት ወሳኝ ነገር አለ፡፡
    ልክ እንደ መጀመሪያዉ ኑዛዜ ሰዉ የፈለገዉን ያህል ህክምናና እንክብካቤ ቢደረግለት ከሞት አያመልጥም፡፡ ሁሉም ዶክተሮች ሞትን አሸንፈዉ ህመምተኛዉን ሰዉ ሊያስጥሉት ፈፅሞ አይችሉም!
    እንዲያዉ ለጊዜዉ ይሞክራሉ እንጂ ዞሮ ዞሮ ሁሉም ወደሞት ነዉ!
    ሁለተኛዉ ደግሞ በህይወት ዘመኔ ስዳክርለትና ስደክምለት የኖርኩት ሃብት አሁን ይዤዉ መሄድ አልችልም፡፡ ገንዘብንና ሀብትን እያሳደዱ መኖር ከንቱና ባዶ የማይጠቅም መሆኑን ተረዳሁ፡፡
    ሶስተኛዉ ደግሞ ወደዚህ አለም ስመጣ በባዶዬ መጥቻለዉ፣ ስሄድም እንዲሁ በባዶዬ! ምንም ሳልይዝ እጄ ባዶ እንደሆነ ነዉ፡፡
    የእናንተም እጣ እንዲሁ ነዉ በባዶህ እንደመጣህ ድምቡሎ ሳትይዝ በባዶህ ትመለሳለህ” አለዉ ይባላል ፡፡
    ውድ የፌስ ቡክ ወዳጆቼ
    የሰው ልጆች ስንባል ነገ ሁሉንም ጥለነው ባዶቻችንን ወደ መቃብር
    ለምንሔደው አለም ለለ መረዳዳት የሚያጨካክነን ነገር ምንድ ነው ? ::
    ለሀገራችን ሌላ ታሪክ መስራት ቢያቅተን እንኳን በሐገራችን ጅምላ ጨራሽ የኮረና ወረርሽኝ ለመከላከል ለሚደረገው የወገን አድን ዘመቻ ያለችንን ለማካፈል አንጨካከን :: በመከራ ቀን የኢትዮጵያን ልጆች አንርሳ ፤ የዛሬ ሰው ብቻ አንሁን ፤ የትላንቱንም እናስብ፤ አንገት የተፈጠረው ዞሮ ለማየት ነውና ።ሰምቶ ማመን ፣ ከተጎዱት መማር አስተዋይነት መሆኑን አንርሳ ። የሰማንያ ዓመት ዕውቀትን ለመገብየት ግድ ሰማንያ ዓመት መኖር የለብንም ። ሰማንያ ዓመት ከኖሩት በትሕትና መጠየቅ ይገባናል ።
    ለማንኛውም ልብ ያለው ልብ ይበል ::
    ጮማዬን ደብቄ ብቻዬን ልበላው
    ጣፋጩን እርጎዬን ሸሽጌ ልጠጣው
    ድርቡን ሸማዬን ደብቄ ልለብሰው
    ደሀ ጎረቤቴን ምንም እንዳያምረው
    "ቸግሮኛል"አልኩት ለአፌም የምቀምሰው
    ጮማዬን ሸሽጌ ማጦቴን ስነግረው
    ደሀ ጎረቤቴን እንባ ተናነቀው
    "እኔ ብሎኝ " አዝኖ ከቤት እደወጣ
    ሽምብራውን ይዞ ሊያካፍለኝ መጣ።
    ድሀ ቆራጡ ::
    እኔም ለዛሬው በዚሁ አበቃሁ በሌላ ዝግጅት እስክንገናኝ ቸር ይግጠመን ::
    አለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ለንደን፣)
    Read more
  • " የግዜና የዘመን ተወቃሽ ትውልድ እንዳንሆን !! "

    የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የሰጡትን ጋዜጣዊ መግለጫ በምሐበራዊ ሚዲያያዎች ተከታትየው ነበር :: በተለይ በመግለጫቸውም ትኩረት ባደረኩበትን ብቻ ላይ የግል አስተየትን መግለፅ እወዳለሁ ::
    " በሀገሪቱ የመጣው ለውጥ ብቸኛ ባለቤት የኢትዮጵያ ህዝብ ስለሆነ ከውጭ የሚገቡ የፖለቲካ ድርጅቶችን የማግለል አካሄድን ሊከተሉ አይገባም " ሲሉ ተናግረዋል።
    እውነት ነው :: በዚህ በኩል ፣አብይ ትክክል ናቸው ::
    ኢትዮጵያ በልባችን ውስጥ ልዩነትነታችንን አዝላ ተሸክማ ፣የምትኖር በልዩነት አንድነትን የምትሰብክ የብዙሐን ህብር ብሔር አምባ የመቻቻል ሐገር ፣ የህብረት ምስክር ፣የሶስት ሽህ ዘመን የገድላት ክምር የታሪክ ማህደር የሰው ዘር መገኛ ፣ የሥልጣኔ ምንጭ ናት ::
    ነገርግን፣ በወቅቱ የጎሳ ሽንሸና ፣መርዘኛ ውጤት ቀስ በቀስ በትውልዱ ውስጥ እንደ ካንሰር ሁኖ ገብቶ ፣ ትልቁን የሐገር ጉዳይ ትተን የእርስ በእርስ ግጭትንና የምሐበራዊ ቀውስ ለማምጣት በትልቁም በትንሹም እየተቆራቆስን የቅዠት ፍልስፍና ጀምረናል ::
    በዚህ ምክኒያት አብይ አድስ ነገር አምጥተው ሐገሪቱን ወደ ተሻለ ስርአት ይዘዋት ሊጏዙ የሚችሉ አይመስለኝም ::
    አዲስ አቅጣጫ በመቀየስ የፍቅርና የሰለም ታላቅ ሐገር ለመገንባት የሚችሉበትን ጊዜ ሁሉ በእኛ አለመስማማት ውድ ጊዚያቸውን እየተሻማን የተበላሸውን ሲያስተካክሉ የነቀልነውን ሲተክሉ ጀንበር ወጥታ ትጠልቃለች ::
    በዚህ ሁለት ቀን እንኳን አዲስ አበባ ላይ የሚደረግውን የመንጋ ፓለቲከኞ ጭፍራዎች ያዙኝ ልቀቁኝ እሪታና ዳንኪራ ልብ ይሰብራል :: የታገለነው አስፓልትና ግንብ ቀለም እየቀባን ልንደባደብ አይደለም :: የሁላችንም ደም አንድ ነው በማለት መተኪ የለላት ህይወታችንን የገበረነው ወደ ነፃነት ተራራ ለመድረስ ነበር ::
    በዚህ ምክኒያት አብይ የሰጡት መግለጫ ወቅታውይና ተገቢም ነው :: " ተነጋግሮ መግባባት መተባበር ሲቻል በተናጠል በመፈክር አሸናፊ መሆን አይቻልም " የሚሉት
    አብይ በዛሬው ጋዜጣዊ መግለጫቸውም በሰንደቅ አላማም ጉዳይ
    የመንግስታቸውን አቋም ግልፅ አድርገው ተናግረዋል ::
    " ባንዲራ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ የሚፈልገው ከሆነ ተመካከሮበትና ድምጽ ሰጥቶ መቀየር ይቻላል "
    ካልሆነ ግን በጉልበት እኔ ባልኩት ብቻ ይሁን የምንል ከሆነ ኢትዮጵያን ማፍረስ ይሆናል ሲሉም አሳስበዋል።
    እርግጥ ነው የኢትዮጵያ ሕዝብ ለነፃነቱና ለሰንደቅ አላማው ቀናኤና ጀግና ለሐገሩ ሲል በጋራ ማንኛውንም መስዋእትነት ለመክፈል ዝግጁ መሆኑ በውጭ አለም ከረጅም ጊዜ ጀምሮ የታወቀ ነው ::
    አባቶቻችን በየዘመናቸው የገጠማቸውን ወራሪ ሐይል መክተው ወቅቱ የሚጠይቃቸውን መስዋዕትነት ከፍለው የሚያውለበልቡት አረንጏዴ ቢጫ ቀይ የነፃነት ምልክት ስለነበር በአደራና በውርስ ተረክበነዋል ::
    ከዚህ በተጨማሪም የጥቁሮች የነፃነትና የትግል አርማ ሆኖ በተለያዩ የአፍሪካ ሐገሮች አሁን ድሩስ ሰንድቅ አላማቸውን አመሳስለው ያውለበልቡታል ::
    ከዚም ባለፈ የአፍሪካ አንድነት ድርጅት በዃላም የአፍሪካ ህብረት ፅፈት ቤት አዲስ አባ ላይ እንዲሆን መወሱኑ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ሕዝብና መንግስት ምን ያህል ክብር እንደተሰጣት የሚገልፅ ነው :: 3.2 ሚሊዮን አመት እድሜ ጠገብ የሆነች ሐገር 100 ሚሊዮን የሚደርስ ከ80 በላይ ብሔር ብሔረሰብ የተለያዩ እምነቶች በመፈቃቀድና በመከባበር በጋራ የሚኖሩባት ሐገር ለዘመናት ሲኖሩባት የአፍሪካን አይደለም የአለምን ትኩርተት የሳበች የድንቅነሽ (የሉሲ) ሐገር የፀረ ኮሎኒያሊዝም ድል አድራጊ ሕዝቦች ዛሬ ስንደቅ አላማ ብርቅ ሆኖባቸው ሊያነታርኩና የጠላት መሰቂያ ሲሆኑ መላውን አፍሪካ ማሳዘኑ አይቀሬ ነው :: ይህ ሰንደቅ አላማ ከኢትዮጵያ አልፎ የአፍሪካ የጥቁሮች የትግል አርማ ለመሆን የበቃ ነው ::
    የሶስት ቀለማት ህብር የሆነው አረንጏዴ ቢጫ ቀይ ቀለም ሰንደቅ አላማ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሐብት ነው ::
    ይህ ሰንደቅ አላማ ማንም እንደፈለገ የሚያውረደው ማንም እንደፈለገ የሚቀይረው ሳይሆን ገና ተከታታይ ትውልድ የሚረከበው ብሔራዊ አርማች ነው ::
    ይህ ሰንደቅ አላማ ልክ እንደ አክሱም እንደ.ላሊበላ ብሔራዊ ቅርስች ነው ::
    በቅድመ ታሪክና በታሪክ ዘመን የኢትዮጵያ መገለጫ በደምና በአጥንት አብሮ የተሰፋ ነው ::
    አባቶቻችን ፀረ ኮሎኒያሊዝምን ሰባብረው ድል ሲመቱ ያውለበልቡት የነበረው የነፃነታቸው ምልክት ነው ::
    ይህ ሰንደቅ አላማ ግልፅ የሆነ የራሱ አደራደር ያለው የራሱ ታሪካዊ ትርጉም ከህዝቦቿ ልዩ ልዩ ትርኢት ፣ ጨዋታ ፣ስነቃል ፣የሐይማኖት የእምነት የጋብቻና የሐዘን ባህላዊ እሴትች ጋር የተጣመረ ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚተላለፍ በቀስተ ዳመና ምስል በሰማይ ላይ የሚታይ የክርስቶስ ባንድራ ነው ::
    ከዚህ አንፃር የበርካታ ብሔር ብሔረሰቦች መገኛ የሆነች ሐገራችን ኢትዮጵያ የዚህ ብርቅየ የሆነ ሰንደቅ አላማ ባለቤት ናት ::
    ወደድንም ጠላንም ብንጠግብም ብንራብም በዚች አብረን በቆምንባት መሬት ላይ ነው የተወለድነው ::
    የምንኖረውም በዚችው ኢትዮጵያ በተባለች ሐገር.ላይ ነው ::
    ኑሯችን የተመሰረተውም ሆነ የወደፊት ተስፋችንን በዚችው እትብታችን በተቀበረባት መሬት ውስጥ ነው ::
    የጠቅላይ ሚኒስትር አብይን አባባል ልዋስና " ስንኖር ኢትዮጵያዊ ስንሞት ኢትዮጵያ ነን" : :
    ፈለግነውም አልፈለግነውም አፈር ትቢያ የምንሆነው በዚችው መሬት ውስጥ ነው :: አንድነታችን በልደትም በኑሮም በሞትም በህይወታችንም ሆኑ በኑሯችን በማንነታችንም እኛ ሁላችንም የኢትዮጵያ መሬት ነን ;:
    ታዲያ እንዳለመታዱል ሆኖ ይህ ትውልድ.የማይደማመጥ የጀግና ጥላቻ ... እስካሁን ድረስ ያለበት ትውልድ ነው :: ታላላቅ የሐገሪቱ መሪዎች የነበሩት በደንቁርና የምናበሻቅጥ ነን ::
    እነዚህ ታሪክ የሚያወሳቸውና የሚያከብራቸው መሪዎች ስናነሳ የአመራር ብቃታቸውና የተጎናፀፉት የሞራል ስብዕና ነው እንጅ የምንናገርላቸው በስማቸው ታቦት ተቀርፆ እናምልክባቸው እያልን አይደለም :: ደጋግመን ደጋግመን የምናዎሳቸው የታሪክን አቅጣጫ ለሐገራቸው ጥቅም እንዲስማማ ለአለምም አንድ አይነት ውጤት አምጥተው አበርክተው ስላለፉ ነው :: ለዚህ በዚህ ፅሁፍ ዘርዝሬ የማልጨርሳቸው ጀግኖች በዎቅቱ በሐገሪቱ የመከራ ቀን በጋራ ዋጋ ከፍለውበት አልፈዋል :: በዚያ የፈተና ወቅት ደግሞ ብዙ ጀግኖች በአንድ ግዜ ማግኜት ያስቀና ነብር :: ስለዚህ የግዜና የዘመን ተወቃሽ ትውልድ እንዳንሆን አብረን ልናስብበትየሚገቡ እጅግ በጣም ብዙ ጉዳዮች ስላሉ ሰከን ብለን ልንደማመጥና ልንከባበር ይገባል ::
    ለዛሬው ዝግጄት ጨረስኩ በሌላ ዝግጅት እስክንገናኝ ቸር ይግጠመን::
    አለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ለንደን)

    Read more
  • ብርሀን ዘ ኢትዮጵያ ........!! ጣይቱ ብጡል (እቴጌ )

    ብርሀን ዘ ኢትዮጵያ ........!! ጣይቱ ብጡል (እቴጌ )

    እንደምን አላችሁልኝ ውድ የፌስ ቡክ ወዳጆቼ :: ለዛሬው አብሪያችሁ የምቆየው ፣ የግዙፍ ሰብዕና ፣ባለቤት በኢትዮጵያ ፣ሴቶች ታሪክ ፣ ውስጥ እንደክዋክብት ብርሐን ታሪካቸውን በአለም የነፃነት ታሪክ መዝገብ ላይ ፣በወርቅ ቀለም ፣ ፅፈው ይችን መከረኛ አለም ከተሰናበቱ አንድ መቶ አመት፣ ስለሞላቸው ፣ ታሪከ ደምም እቴጌ፣ ጣይቱ ብጡል ብርሐን ዘኢትዮጵያን ፣ የህይወት ጉዞ አስቃኛችዃለሁ :: በጥቁሩ ዓለም ውስጥ በነፃነቷ ኮርታ ለሌሎቹ ምሳሌ የምትሆን ኢትዮጵያን ፣ ከምንይልክ ጋር ተረክበው ፣ ሐገራቸውን በጦርነተም ፣ በፓለቲካውም ፣ በመንፈሳዊ ጠንክራ፣ ለአለም እንድትታይ እስከ እለተሞታቸው ድረስ የደከሙት ብርሀን ዘኢትዮጵያ ጣይቱ ብጡል ናቸው :: 
    ብርሐን ዘኢትዮጵያ ጣይቱ ፣ በጦርነትም ወቅት ፣ ለአርበኛው ሁሉ ማነቃቂያ ለወዶቹም፣ ለሴቶቹም፣ ፅናትና ተምሳሌት ሲሆኑ ፣ አገር ና ታሪካቸውን ከቅኝ አገዛዝ ወራሪ ፣ የተከላከሉ ፣ የውጫሌን ውል ተፀይፈው ኢትዮጵያ አትቀበልም በማለት ፣ በአቋማቸው ፀንተው አለምን ያስደመውን ፣ ውሳኔ በማስተላለፍ የአድዋውን ጦርነት ከምንይልክ ጋር የመሩ ፣ የጦር ፊታውውራሪ ጣይቱ ብጡል ብርሐን ዘኢትዮጵያ ናቸው ::
    እቴጌ ጣይቱ ብጡል ፣ በነሐሴ አስራ ሁለት ሺህ ስምንት መቶ ሰላሳ ሁለት ፣ በጎንደር ክፍለ ሐገር በደብረ ታቦር ከተማ ተወለዱ :: በደብረ ታቦር እየሱስ ቤተክርስቲያን ክርስትና ተነሱ ::ብላቴን ጌታ ህሩይ በአሳተሙት መፃፋቸው ላይ 
    “ጣይቱ በምትባል ሴት የኢትዮጵያ መንግስት ታላቅ ይሆናል እየተባለ ሲነገር ይኖር ነበርና ከአፄ ምኒልክ አስቀድሞ የነበሩ አንዳንድ ነገሥታት ስሟ ጣይቱ የምትባል ሴት እየፈለጉ ማግባት ጀምረው ነበር። ነግር ግን ጊዜው አልደረሰም ነበርና አልሆነላቸውም። ዘመኑ በደረሰ ጊዜ ግን አፄ ምኒልክ እቴጌ ጣይቱን አገቡ። " ይላሉ :: ኢትዮጵያን ታላቅ ለማድረግ ትእንቢት ሲነገር ላቸው የነበሩት ጣይቱ ብጡል ጊዜው በደረሰ ግዜ ዳግማዊ ምንይልክ 
    የንጉሰነገስት ዘውድ ጭነው ንጉሰነገስት ዘኢትዮጵያ ሲባሉ ፣ በሶስተኛው ቀን ጥቅምት ሀያ ሰባት 1882 ሐምሳ አንድ ጊዜ መድፍና ለሰባት ስአት የፈጀ ተኩስ እየተኮሰላቸው የተመሰገኑት ቆንጆዋ የደስ ደስ ያላቸው ደማሟ ብልህና ፣ ጀግናዋ የኢትዮጵያን የዘመናዊ አዋላጅ ጣይቱ ብጡል በቅዱስ ቁርባን ምንይልክን አግብተው እቴጌ ጣይቱ ብርሐን ዘኢትዮጵያ የሚል የክብር ስም ተሰጣቸው :: በዚሁ ስም የክብር ምሐተም ተቀረፀላቸው ::
    ከምንይልክ የአራት አመት ታላቅ የነበሩት ጣይቱ ብጡል የተወለዱት በንሐሴ አስራ ሁለት ሲሆን ምን ይልክም የተወለዱት ነሀሴ አስራ ሁለት ነው
    ጣይቱ ብጡል በኢትዮጵያ ፓለቲካ አስተዳደር አንፃር በነበራቸው ችሎታ በታሪክ ተመራማሪዎች ዘንድ ተደናቂነትን ሲያተርፍላቸው 
    በየግዜው ይነሱ በነበሩት የሐገር ጉዳዮች ላይ ይይዙት የነበረው አቋም ፣ ይሰጡት የነበረው ውሳኔ ፣ ያቀርቡት የነበረው ብልሐት፣ ያስተላልፉት የነበረው ትዕዛዝ ፣ ሙሉ በሙሉ የሚኒሊክን ተቀባይነት ያገኜ ነበረ :: እነዚህን ታሪካዊ የህይወት ፣ ጉዞ ሂደቶች በፖለቲካው በወታደራዊ ፣ ማህበራዊ ኑሮ ውስጥ፣ ከፍተኛ ብሩህ ሚና ለመጫወት ያስቻላቸው ፣ ብዙ ሁኔታዎች ነበሩ ::ከዚያም ባለፈ ከፍተኛ የድፕሎማትነት ችሎታ የነበራቸው አስተዋይነት ታጋሽነት ያጣመሩ ናቸው ::
    እቴጌ ጣይቱ ብርሐን ፣ ዛሬ በኢትዮጵያ ተደናቂነትን ፣ ካላቸው ታሪካዊ ቅርሶች ውስጥ አንዱ ፣ የሆነውን ስመ ጥሩውን ፣ የእንጦጦ ማሪያም ቤተክርስቲያንን ፣ ያስገነቡ ሲሆን በጠቅላላው ፣ አስራ ስድስት አብያተ ቤተክርስቲያንን ፣ ማሳነፃቸውን በተአምረ ማርያም እና በወንጌሉ ፣ ዳር ተፅፎላቸው ይገኛል :: ከዚህ በተጨማሪም የአፍሪካን መዲና ፣ የሆነችውን ፣ አዲስ አበባ ከተማን የቆረቆሩ እውቅ ምሐንዲስ ሲሆኑ፣ ኢትዮጵያን ዘመናዊ ለማድረግ በተደረገው ጥረት ሁሉ ፣ የምንይልክ ቀኝ እጅ ሆነው ፣ ጥርጊያውን አፅድተው አውራ ጎዳናውን የከፈቱት ብርሐን ዘኢትዮጵያ ጣይቱ ብጡል ናቸው :: በነገራችን ላይ ጣይቱ ብጡል ያልተሳተፉበት ልማት አልነበረም :: ስልኩም ባቡሩም ኤሌትሪኩም ፊልሙም ቧንቧ ፣ ውሐውም መኪናውም ፣ ት/ቤቱም ፣ ሆስፒታሉም ፣ ሆቴሉም ሆነ መንገድ መገንባትና ፣ ዘመናዊ መሆን የጀመረው ፣ በጣይቱና ፣ በምንይልክ ግዜ ነው ;: በዚህ ባለንበት ዘመን ሁነን ከቀደምት ጀግኖቻችን ታሪክ ገድል ስንፈትሽ ፣ በኢትዮጵያ ሴቶች ታሪክ ውስጥ ፣ ኢትዮጵያን ተረክቦ ለማቆም ፣ በከተፈለው መስዋዕትነት ፣ ጭምር ትልቁን ስፍራ የያዙት ፣ የአድዋዋ ጀግና ፣ ጣይቱ ብጡል ብርሐን ዘኢትዮጵያ አንዷ ናቸው ::
    ጣይቱ ብጡል ብርሐን ፣ ዘኢትዮጵያ ፣ የኢትዮጵያ ፣ልጆች በባእድ አገዛዝ ፣ ስር ተንበርክከው ፣ባርነትን እንዳይቀበሉና ፣ ሐገራቸውን እንዳይነጠቁ ፣ ወረራን እንዲመክቱና ፣ ሉአላዊ ሐገራቸውን እንዲጠብቁ ፣ ዳርደንበራቸውን እንዲያስከብሩና ፣ ውስብስብ የነበረውን ጦርነት ፣ በአሸናፊነት እንዲወጡ ፣ ሶስት ሺህ እግረኛ ጦር ስድስት ሽህ ፈረሰኛ ጦር እየመሩ ታቦት አስይዘው የአድዋውን ጦርነቱን በነፍጥም ፣ በመንፈስም የመሩ ናቸው :: ከዚህ አኳያ የኛ ትውልድ ማወቅ የሚገባን ፣ ቁም ነገር ቢኖር ፣ ያለ እምዬ ምንይልክ ያለ ጣይቱ ብጡል ፣ ያለ ባልቻ አባ ነፍሶ ፣ ያለ አሉላ አባ ነጋ ፣
    ያለ ገበየሁ ጎራ ፣ ወ..ዘ..ተ.የአድዋውን ጦርነት ማሸነፍ እንደማይቻል እንኳን እኛ ጠላቶቻችን መስክረዋል :: እኛ ባልተፈጠርንበት ዘመን እነዚህ የኢትዮጵያ መከታ ነበሩ :: ታዲያ የነዚህን ጀግኖችን ታሪክ ስንደብቅ ፣ ኢትዮጵያንን እየደብቅናት ነው :: የነ ጣይቱ ብጡል ታሪክ ስናጠፋ ፣ ኢትዮጵያን እያጠፋናት ነው :: የነእዚህ ጀግኖች ሐውልት እንዳይቆም ስንከለክል ፣ ከሐገር ጠላቶች ከነ ሞሶለኒ ፣ ብምን ልንሻል እንችላለን ::
    ኢትዮጵያን ለማቆየት ተከታታይ የመስዋእትነት ፣ ውርስ አለ :: በየዘመኑ የሚነሱብን ጠላቶች የየዘመኑ ትውልድ አንገት ለአንገት እየተናነቀ ወድቋል :: የመሞት ውርስ ሳይቀር ተረካክበናል:: ታዲያ እኛ መሞት ቢያቅተን ለኢትዮጵያ ክብር የሞቱላትን ፣ ጀግኖቻችንን ታሪክ ለትውልድ እንዳይተላለፍ ፣ ቅርስ አልባ እንድንሆን የሚከለክሉን ፣ እነማን ናቸው :: እንደኔ እንደኔ ለነገ ቅርስ ለማቆም.ፍቃደኞች ካልሆን ዛሬ ጀግና አንፈጥርም :: ይህ ትውልድ ክፉ ትውልድ መሆን የለበትም:: ካለንበት የቁም እንቅልፍ ልንባንን ይገባናል :: ኢትዮጵያ ዊ የሚለውን ፣ የዜግነት መለያ የምንቀበለው ፣ በኩራትና በራስ የመተማመን መንፈስ ፣ መሆን አለበት ::
    አሁን አዲስ ራኤ አንስተን በመደመር ፣ ለሁላችንም የምትበቃ ሐገር እንደ አድዋ ጀግኖች እጅ ለእጅ ተያይዘን ፣ ኢትዮጵያ መገንባት ሲገባን ዛሬም እንደትናንትናው የዘር ፣ የቋንቋ ቡቲቶ ፣ እየጎተትን ከአንድነታችን ፣ይልቅ የምንለያይበትን ፣ ክር ለመበጠስ እንደረደራለን :: ይህ ትውልድ ኢትዮጵያውነቱ ለማክሰም የታሪክ እምነቱን የባህል እሴቱን ለማውደም ሞራሉን ሐገራዊ ስሜቱን ወገናዊ ፍቅሩን የጋራ መተሳሰሩን፣ለማላላት የኢትዮጵያ ጠላቶች ተጠቅመውበታል :: ከአሁን በዃላ ግን በላያችን ላይ የሚጎሰምብን የመንጋ ፓለቲከኞች የሞት ነጋሪት አናዳምጥም :: ጣይቱ ብጡል ብርሐን ዘኢትዮጵያ ፣ ጠላት እንኳን ሊደመስሰው ፣ ያልቻለውንና የማይችለውን ፣ የዘመናዊነት ስም ፣ እና የጀግንነት ዝና ለሐገራቸው አትርፈዋል :: በርህራሔና በልግስና ፣ እጅግ የተወደዱ እቴጌ ሲሆኑ በቆሙለት አላማ ፣ የሚፈታተን ጉዳይ ፣ በሚፉጠርበት ጊዜ አንደበተ ርእቱ በመሆናቸው ፣ ቆራጥ አቋም ያላቸው ፣ የማይወላውሉ :: ተግባራቸው : ውሳኒያቸውን : ግልፅ አድርገው : ማስቀመጥ የሚወዱ በመሆናቸው ከምንይልክ ጋር ተደጋግፈው ፣ በጦርም በሰላምም ጊዜ እኩል በመኖር ፣ እቴጌ የእህትና የሚስት ፣ የንግስትነት ሚናቸውን ተወተዋል :: የሆነ ሆኖ እስከአሁን ፣ ድረስ የእቴጌ ጣይቱ ብጡል ባህሪና ጀግንነት በትክክል ፣ የሚወክል ቃል በእኔም ፣በታሪክ ተመራማሪዎችም አልተገኜላቸውም ::
    ሐይመኖተኛዋ በገና ደርዳሪዋ ፣ የሐገራቸውን ደህንነት ምንግዜም የሚስቀድሙት ፣ አስተዋይና ቆራጧ ፣ ብርሐን ዘኢትዮጵያ ፣ የካቲት 4 ቀን 1910 ሰኞ በመንፈቀ ለሊት ፣ የስም ማስጠሪያ የሚሆን ከአብራካቸው አንድ ልጅ እኳን ፣ ሳይተኩ ምሐኗ ብርሐን ዘኢትዮጵያ ይህችን መከረኛ አለም ተሰናብቱ :: አስከሬናቸውም በወርቅ ሐረግ በተከበበ የእንጨት ሳጥን ውስጥ ፣ ከገባ በዃላ ፣ በመንበረ ፀሐይ እንጦጦ ማርያም ፣ ቤት ውስጥ በታላቅ ክብር አረፈ::
    ሆኖም ግን ፣ ንግስት ዘውዲቱ በታህሳስ 1920 የአፄ ምንይልክን አፅም ፣ ከቤተ መንግስት አስወጥተው ፣ በባእታ ቤተክርስቲያን ውስጥ ሲያኖሩ 
    የእቴጌን የንዛዜ ቃል አክብረው ፣ የብርሐን ዘኢትዮጵያ ጣይቱ ብጡል አፅም ከእንጦጦ ማርያም ወርዶ ፣ በባእተ ቤተክርስቲያን ከታላቁ የአድዋው ጦር መሪ ፣ ከኢትዮጵያ ንጉሰነገስት ፣ ከዳግማዊ ምንይልክ ጎን ፣ በባእታ ቤተክርስቲያን ፣ በክብር አርፎ ይገኛል ::
    ጣይቱ ብጡል ዘኢትዮጵያ ዝንት አለም ፣ ከመቃብር በላይ እንደተሰቀለ ፋኖስ ፣ ከሐጉር ሐጉር ፣ እያንፀባረቀ የአድዋውን ፣ ገድል እየመሰከረ፣ ለኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን ፣ የአፍሪካ የነፃነት ምልክት ሆኖ ፣ ለዘላለም የሚኖር ታሪክ ሰርተው ቢያልፉም ፣ እስከ አሁን ድረስ ስማቸውን የሚያስጠራ ፣ አንድም ፣ ሐውልት ሳይሰራላቸው በመቅረቱ፣ በታሪክ ተመራማሪዎችና ፣ በቅርስ ተቆርቋሪዎች ፣
    በኩል ከፍተኛ ቅሬታን ቢቀሰቅስም ፣ አንፀባራቂው የአድዋው ታሪክ እንዳይነሳና የአባቶቻችን ታሪክ ፣ ለትውልድ እንዳይተላለፍ ፣ በማይፈልጉ፣ኢትዮጵያን በሚጠሉ ክፉ ሰዎች ምክኒያት እስከ አሁን ድረስ ለክብራቸው የሚመጥን ሐውልት አልቆመላቸውም :: ሆኖም ግን ይዋል ይደር እንጅ ኢትዮጵያን በክፉ የሚያይ ሁሉ መጨረሻውን ታሪክ ቁጭ ብለን እያሳየን ስለሆነ ዋጋቸውን እንደስራቸው እንደሚቀበሉ እርግጠኛ ብሆንም ፣ አንድ ቀን ግን፣ እውነተኛ የኢትዮጵያ ልጆች ተባብረው ፣ ለምሐኗ የአድዋ ጀግና ሐውልቷን እንደሚቆሙላት ህልም አለኝ ::
    ለዛሬው ግን ይህን ታሪክ ስፅፍ እንደከዚህ ቀደሙ ደስ ብሎኝ ሙሉ የመንፈስ ኩራት እየተሰማኝ ሳይሆን በብዕሬ ላይ በሚፈሰው ቀለም ሳይሆን በደሜ የፃፍኩት ያህል ጥቃት እያመመኝና እንባ እየተናነቀኝ ነበር የፃፍኩት !!! ::
    ለዛሬው በዚሁ አበቃሁ በሌላ ዝግጅት እስክንገናኝ ቸር ይግጠመን ::
    አለባቸው ደሳለኝ አበሻ ( ለንደን)
    ሸር በማደርገዎ ልባዊ አድናቆቴ ይድረስልኝ

    Image may contain: 1 person
     
    Read more
  • ቤተ ክርስቲያኗ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ላመጡት እርቅና ሰላም ልዩ ሽልማት አበረከተች

    ቤተ ክርስቲያኗ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ላመጡት እርቅና ሰላም ልዩ ሽልማት አበረከተች

    አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 4፣ 2010 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ላመጡት ሰላምና እርቅ ልዩ ሽልማት አበረከተች።

    Image may contain: 4 people, people smiling, people standing

    ቤተ ክርስቲያኗ ልዩ ሽልማቱን ያበረከተችው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል ብሎም በምስራቅ አፍሪካ ቀጠና ሰላም እንዲመጣ አድርገዋል በሚል ነው።

    ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ሽልማቱን በተረከቡበት ወቅትም፥ ሽልማቱ ያለእረፍት ይህ ነገር እንዲመጣ ሲታገሉ ለነበሩ እና ይህ ለውጥ እንዲመጣ ሲፀልዩ የነበሩትን በሙሉ የሚገባ ነው ማለታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ልዩ ሀላፊ አቶ ፍፁም አረጋ በትዊተር ገጻቸው አስታውቀዋል።

    በሙለታ መንገሻ

    Source: Fana Broadcasting

    Read more

Latest Articles

Most Popular