Habesha

  • " ዲሽታግና ".....አዳም ወንድሜ ...!!

    በአንድ ወር ውስጥ የ8.4 ሚሊዮን የተመልካች ቱጃር ሆነ ::

     

      ከአለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ለንደን)                       

     

    የሙዚቃው ኢንዱስትሪ እጅግ በጣም ፈጣን እድገት የሚታይበት፣ ተለዋዋጭና ከፍተኛ ፉክክር ያለበት በመሆኑ ብዙ ድምፃውያን የሙዚቃ ምርጫቻው እንደአሳታሚው ፍላጎት የሚለወጥበትም ጊዜ ያጋጥማቸዋል ::  በዚህ ምክኒያት ዛሬ ተወዳጅ የሆነ ሙዚቃ ቶሎ ይሰለችና፤ አሮጌ ሆኖ ሸልፍ ላይ ይቀመጣል ::  

    አንድ ሙዚቃ ተወዳጅ መሆኑንና አለመሆኑን የሚወስነው  በሙዚቃው አድማጭ በመሆኑ  ሙዚቃውን  የምንመርጥበት መስፈርት ደግሞ ብዙ ነው ::  አንዳንዶቻችን የሙዚቃው ቅንብርና የድምፃዊያኑን ቅላፄ ስናደንቅ ሌሎቻችን  ደግሞ ምቱ ደስ ስላለንና  ግጥሞቹ  ወይንም የሥነ ምግባር እሴቶቻችንም  ግምት ውስጥ  አስገብተን ስለተመቸን  ከሙዚቃው  ቃና ከፍተኛ ኃይል ይልቅ  በስሜታችን ላይ ጥልቅ የሆነ ተጽዕኖ የሚያሳድረው   ጠብቅ፤ የሕይወት ግንኙነት የሚኖረው ግጥሙ ሆኖ እናገኜዋለን  :: 

    ሙዚቃ በሰዎች ጤና እና ባህሪ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ሊኖረው ይችላል የሚለው የባለሞያዎች ምክር እንደተጠበቀ ሆኖ በአለም አቀፍ 

     ተወዳጅ እንዲሆንና በብዛት  እንዲደመጥ እንዲሸጥ ምክኒያት የሚሆነው ግን የወጣቱ  ተሳትፎ ነው ::  በተለይ የግጥምና የዜማ ደራሲዎችም ቢሆኑ በበኩላችው  የሰዎችን ስሜት የሚኮረኩሩ ማለትም በተስፋቸው፣ በሚያልሙት ነገርና በውስጣዊ ስሜታቸው ዙሪያ የሚያጠነጥኑ ስንኞችን ለማዘጋጀት ስለሚጥሩ ወጣቱ ለሙዚቃው ኢንዱስትሪ ማደግ ትልቅ አስተዎፅዎ አድርጏል ::

    ሆኖም ግን በብዙዎች ዘንድ ተቀባይነት ማግኘት የሚችሉና  እድሜ ጠገብ ሆነው የሚዘልቁ በጣም ጥቂት ድምፃዊያን ካልሆኑ በቀር አብዛኛዎቹ ሞያቸውን እርግፍ አርገው  በመተው መድረኩን ጥለው በመውጣት በተለያየ ሞያ ተሰማርተው ይገኛሉ :: ::

     እንደምን አላችሁልኝ ውድ የፌስ ቡክ ወዳጆቼ 

    ለዛሬው ይዤላችሁ የምቀርበው በዩቲዩብ ተለቆ በአንድ ወር እድሜ ውስጥ የ8.4 ተመልካች ቱጃር ስለሆነው  የድምፃዊ ታሪኩ ዲሽታግና

    የኦሪስ ብሔረሰብ ዘፈን ነው ::

    በቅድሚያ የሙዚቃ ግጥሞቹ ሲዘጋጁ የሰውን ልጅ ስሜትና የልብ ትርታ ለመግዛት በፍጥነትና  በዝግመት እየጠበቁ በምርጥ የሙዚቃ ቃናን ተከሽነው አዕምሮአችንን ጠልቀው ለመንካት ለማዝናናት ኃይል እንዲኖራቸው ተደርገው ስለተዘጋጁ አይረሴነት ይዘት አላቸው ::

    በግጥሙ ስንኝና በሙዚቃው ቅንብር ውስጥ የተውኔት ጥበብ፣ይታይበታል ::  

     

    ዲሽታግና የአሪ ብሔረሰብ አዲስ ዓመት ወይም ዘመን መለወጫ ነው። ዲሽታግና አብረን እንብላ፣ አብረን እንጠጣ፣ የተጣሉትን እናስታርቅ ፣ ለሌላቸው እንስጥ፣ እንደጋገፍ ማለት ነው።

      ዲሽታግና  አድማጩን በመወክልና የስንኙ ተዋናይ እንድንሆን የሚደርግ  ሲሆን በሙዚቃው ምት እንቅስቃሴ መላውን የሰውነት አካል እያፍታታ ሲደመጥ ደስ በተሰኙና ቀለል ባሉ ግጥሞቹ እኛንም ሌሎቻችንንም እርስ በእርስ እንድንተያይ  የታሪኩ ባለቤቶች ሁላችንም በማድረግ የተሸሸጉ በርከታ ማንነትን ወደ አንድነት በማምጣት ዘፈኑን አጏጊ አድርጎ እንድንቀላቀልና እራሳችንን እንድንጠይቅ ልብ እንድንገዛ ጭምር በማድረግ ያሳትፋል :': 

    በሌላ አኳያ ዘፈኑ ከሙዚቃው ጋር ተስማምቶ ድምፃዊ ታሪኩ ጋንኪሲ ሊገልፀው  የፈለገውን ፍሬ ነገር   በሚገርም ጥበብ  ለሁሉም የሰው ዘር  እንደሚጥቅም አድርጎ በመልዕክትነቱ  ለማስተላለፍ ችሏል :: 

     በነገራችን ላይ ሙዚቃ በቴክኒክ ቅንብር የዳበረ መሆን ስለሚገባው ድምፃዊው የሚጠበቅበትን ድርሻ በፈጣራው ውስጥ እነዚህን ቴክኒኮች ተጠቅሞ መልዕክቱን አግዝፎና አጉልቶ ሊያስደምጠን ሲችል ብቻ ነውየተዋጣለት ነው የምንለው ::

     

    ዲሽታግና  ስንኙቹ ባይታወር የሚያደርጉ ሳይሆን በምሳሌነት የተጠቀሰው አዳም ወንድሜ ሕይዋን እህቴ  የሰውን ልጅ አፈጣጠር    ተመርኮዞው በሀይማኖትና በዘር ለሚናከስ ማሕበረሰብ በጥልቀት እራሱን እንዲፈትሽ አግዝፈው የሚያስገነዝቡ የፈጠራ ተልእኳቸውን  የሚያሳዩ ናቸው    :: 

    ዲሽታግና  ከዚህም በላቀ ደረጃ አንድን የ10 አመት የጎዳና ታዳጊ ወጣት አቡሽን  ከአደንዛዥ ሱስ ያላቀቀ  ከእውነተኛ የሰው ልጅ ውስጣዊ ስሜት ጋር የጠበቀ ዝምድና ያስገነዘበና የተፈጥሮን ዳኝነት የእውኑን አለም እውነታ በገሀድ ያሳየ በመሆኑ የሕይወት  ሚስጥራዊ ተልዕኮ አለው ማለት ይቻላል :: 

    ዲሽታግና በችግርና በሀዘን የተቆራመደን ታዳጊ ከትካዜና ከቀዘቀዘ ሕይወት በጥልቀት ገብቶ  የብቸኝነት ጥላውን ገፎ ዝምታን አሰብሮ

    በሞቀ ፈገግታ ሽመሉን አስጨብጦ ዳንኬራ ማስመታት ብቻ ሳይሆን ከጎዳና አንስቶ ሕይወቱን ቀይሮታል :: 

    ዲሽታግና በዚህና በብዙ.ምክኒያት ድምጻዊው ታሪኩ ጋንኪሲ

    ማንነትን ያሳየንና የእሱነቱ መገለጫ  ውስጣዊ የፈጠራ ባሕሪውን ጭምር  ሁለተናዊ አስተዋይነቱን አጉልቶ ሊያስነብበን ችሏል  ::

    በበኩሌ የትያትር ጥበብንና የፊልምን ቴክኒዎለጂ አድናቂ እንጅ  ገፋ በሙዚቃ ስራዎችን ላይ ስለማልሳተፍ በግርድፉ ካልሆነ በቀር ብዙም የጠለቀ እውቀት የለኝም ::

    ቢሆንም  በአንድ ወር ውስጥ ከ8..4  ሚሊየን በላይ ተመልካቾችን ያገኘውን ዲሽታግና አለማድነቅ አይቻልም ::

    ቀደም ብየ ከመግቢያዬ ላይ እንደገለፅኩላችሁ ድምፃዊው ታሪኩ ጋንኪሲ በቀላል ስነግጥም በውስጡ የፀነሰውን ሐሳብ ይዞ ለቃላቱ ሳይጨነቅ በዜይባዊ አነጋገሮች አዚሞ ሕብረ ብሔራዊ ቀለም ሰቶታል :: የመጨረሻውን እፁብ፣ድንቅ ከሚሰኙ የይዘትና ቅርፅ ደረጃ ላይ ለመድረስ ማቋረጥ ያለበትን ውስብስብ ሒደት አልፎ ድምፃዊ ታሪኩ በአንድ ነጠላ ዘፈን አንድ የሙዚቃ ሐውልት ቀርፆ አቁሞ አሳይቶናል  ::

    ለዛሬው የጎዳናውን አቡሽና  ድምጻዊው ታሪኩ ጋንኪሲ መልካም እድል የተመኜሁ ዝግጅቴን በዚሁ አበቃሁ :: የተረፈውን እናንተ ጨምሩበት 

     በሌላ ዝግጅት እስክንገኝ ፣ እድሜ ይስጠን ጤና ይስጠን  እሩቅ ካሉት ቅርብም ካሉት ቸር ያሰማን  ደቡብ ፣ ሰሜን ፣ ምዕራብ ፣ ምስራቅ ፣ በቸር አድሮ በቸር ይንጋ

     

    አለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ለንደን)

    Read more
  • የመጨረሻዋ ስዓት !!

    " የመጨረሻዋ ስዓት !! "
    " ከእያንዳንዱ ብርሀን ጀርባ ጨለማ እንዳለ አስተውል፡፡ ያለህበት ብርሀን ዘላቂ ይሆንልህ ዘንድ መልካም ነገሮችን ብቻ አድርግ፡፡
    ክፋት ካከልክበት ከጨለማው ስር ትወድቅና ታሪክ በበጎ አያነሳህም
    ከአለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ለንደ)
    የሰማንያ ዓመት ዕውቀትን ለመገብየት ግድ ሰማንያ ዓመት መኖር የለብንም ። ሰማንያ ዓመት ከኖሩት በትሕትና መጠየቅ ወይንም የታሪክ ድርሳናትን መፈተሽ ይገባናል ።
    የአለማችን ታላላቅ ሰዎች ፀሀይ ስታዘቀዝቅባቸው፣ ጀንበር ሳትጠልቅባቸው በፊት የዚችን ከንቱ ዓለም የመጨረሻዋ ስአት ላይ የሚገርም ስንብት ያደርጋሉ :: ይህ ታሪክ ሲፈፀም ላላዩት ላልሰሙት ታሪክ ምስክርነቱን ሊሰጥ ዛሬ በፊታችሁ ቆሟል ::
    ካነበብኩት አንድ ለመንገድ ልበላችሁ
    ታላቁ አሌክሳንደር በህይወት ዘመኑ ብዙ መንግስታትንና ሀገሮችን በቁጥጥሩ ስር ያደረገ ጀግና ንጉስ ነበር፡፡ አንድ ጊዜ ብዙ ሀገራትን ድል አድርጎ ወደሃገሩ እየተመለሰ ሳለ በጣም አመመዉ፡፡
    የኔ የሚላቸዉ ጀኔራሎቹንና ቁልፍ ሰዎችም እንዲያርፍና ህክምና እንዲከታተል ማድረግ ጀመሩ፡፡ ነገር ግን የሱ ህመም ከቀን ወደቀን እየባሰና ወደሞት አፋፍ እየቀረበ መጣ፡፡
    አንድ ቀን ግን ህመሙ እጅግ ከብዶ በመምጣቱ አሌክሳንደር እንደማይድን አዉቆታል፡፡ ጄነራሎቹን ሁሉ አስጠርቶ ኑዛዜ መናዘዝ ጀመረ... “ስሙኝ...ከደቂቃ በኋላ ወደማልመለስበት እሄዳለሁ ነገር ግን ስሞት ሶስት ነገሮች እንድታደርጉልኝ እፈልጋለሁ አላቸዉ፡፡
    • የመጀመሪያዉ የመቃብር ሳጥኔ እኔን ሲያክሙኝ የነበሩ ዶክተሮች ብቻ ተሸክመዉ ወስደዉ እንዲቀብሩኝ
    • ሁለተኛዉ ወደ መቀበሪያዬ ቦታ የሚወስደዉ መንገድ በወርቅና በከበረ ድንጋይ እንዲሰራ
    • ሶስተኛዉ ደግሞ ሁለቱም እጆቼ ከመቃብር ሳጥኑ ዉጪ እንዲታዩ አዝዣለሁ ብሎ የመጨረሻዎቹን ትንፋሾች መሳብ ጀመረ፡፡
    የንግግሩን ግራ አጋቢነት የከበቡት ዶክተሮችና አገልጋዬች ባይረዱትም ንጉስ ነዉና ሁሉም ዝም ብለዉ እሺታቸዉን ገለፁ፡፡ ነገር ግን በዚህ ግራ የገባዉ የቅርቡ ጀነራል ንጉሱን እንደምንም ብሎ ጠየቀው
    “ንጉስ ሆይ ሶስቱ ኑዛዜህ አልገባኝምና እባክህ ቢቻልህ ምን ማለት እንደሆነ ብትነግረኝ?” ንጉሱም እንዲህ አለዉ
    “ሁሉም ሰዉ እንዲያዉቅልኝ የምፈልገዉ ሶስት ወሳኝ ነገር አለ፡፡
    ልክ እንደ መጀመሪያዉ ኑዛዜ ሰዉ የፈለገዉን ያህል ህክምናና እንክብካቤ ቢደረግለት ከሞት አያመልጥም፡፡ ሁሉም ዶክተሮች ሞትን አሸንፈዉ ህመምተኛዉን ሰዉ ሊያስጥሉት ፈፅሞ አይችሉም!
    እንዲያዉ ለጊዜዉ ይሞክራሉ እንጂ ዞሮ ዞሮ ሁሉም ወደሞት ነዉ!
    ሁለተኛዉ ደግሞ በህይወት ዘመኔ ስዳክርለትና ስደክምለት የኖርኩት ሃብት አሁን ይዤዉ መሄድ አልችልም፡፡ ገንዘብንና ሀብትን እያሳደዱ መኖር ከንቱና ባዶ የማይጠቅም መሆኑን ተረዳሁ፡፡
    ሶስተኛዉ ደግሞ ወደዚህ አለም ስመጣ በባዶዬ መጥቻለዉ፣ ስሄድም እንዲሁ በባዶዬ! ምንም ሳልይዝ እጄ ባዶ እንደሆነ ነዉ፡፡
    የእናንተም እጣ እንዲሁ ነዉ በባዶህ እንደመጣህ ድምቡሎ ሳትይዝ በባዶህ ትመለሳለህ” አለዉ ይባላል ፡፡
    ውድ የፌስ ቡክ ወዳጆቼ
    የሰው ልጆች ስንባል ነገ ሁሉንም ጥለነው ባዶቻችንን ወደ መቃብር
    ለምንሔደው አለም ለለ መረዳዳት የሚያጨካክነን ነገር ምንድ ነው ? ::
    ለሀገራችን ሌላ ታሪክ መስራት ቢያቅተን እንኳን በሐገራችን ጅምላ ጨራሽ የኮረና ወረርሽኝ ለመከላከል ለሚደረገው የወገን አድን ዘመቻ ያለችንን ለማካፈል አንጨካከን :: በመከራ ቀን የኢትዮጵያን ልጆች አንርሳ ፤ የዛሬ ሰው ብቻ አንሁን ፤ የትላንቱንም እናስብ፤ አንገት የተፈጠረው ዞሮ ለማየት ነውና ።ሰምቶ ማመን ፣ ከተጎዱት መማር አስተዋይነት መሆኑን አንርሳ ። የሰማንያ ዓመት ዕውቀትን ለመገብየት ግድ ሰማንያ ዓመት መኖር የለብንም ። ሰማንያ ዓመት ከኖሩት በትሕትና መጠየቅ ይገባናል ።
    ለማንኛውም ልብ ያለው ልብ ይበል ::
    ጮማዬን ደብቄ ብቻዬን ልበላው
    ጣፋጩን እርጎዬን ሸሽጌ ልጠጣው
    ድርቡን ሸማዬን ደብቄ ልለብሰው
    ደሀ ጎረቤቴን ምንም እንዳያምረው
    "ቸግሮኛል"አልኩት ለአፌም የምቀምሰው
    ጮማዬን ሸሽጌ ማጦቴን ስነግረው
    ደሀ ጎረቤቴን እንባ ተናነቀው
    "እኔ ብሎኝ " አዝኖ ከቤት እደወጣ
    ሽምብራውን ይዞ ሊያካፍለኝ መጣ።
    ድሀ ቆራጡ ::
    እኔም ለዛሬው በዚሁ አበቃሁ በሌላ ዝግጅት እስክንገናኝ ቸር ይግጠመን ::
    አለባቸው ደሳለኝ አበሻ (ለንደን፣)
    Read more

Latest Articles

Most Popular